»

እንደተቀበልኩት ምህረት እንደቸርነትህ ብዛት እንዳገለግልህ እርዳኝ ጌታ ሆይ ስጠኝ የመንፈስን እሳት"-በዚህ ዌብሎግ እውነተኛው የጌታ ኢየሱስ ባሪያ ተስፋዬ ጋቢሶ ይታወስ ዘንድ ወሰንን።This weblog has been dedicated to Tesfaye Gabiso,the faithful servant of The Lord.

አለምልመው

አባት ሆይ ይህን ብላቴና ባርከው አለምልመው ቀድሰው::


ጌታ ሆይ ስለዚህ ወንድማችን ኤልያስ እናመሰግንሃለን:: በኢንተርኔት ፣በከተማ በጎዳናው ፣በቤተክርስቲያን ሁሉ ያገለግላል::

ጌታ ሆይ ይህ ብላቴና ቅኔ ሲቀኝ፣ምሳሌ ሲነግረን፣መዝሙርም ሲዘምር ፤ለስምህም ያለውን ፍቅር፣ለቤተመቅደስህም ያለውን ቅናት ፣ለሕዝቦች ህም ያለውን በጎ ልቡና እናያለን::

ሰውን ሳያይ ከሰውም ምንም ሳይጠብቅ እንዘምር እንቀኝ እንመስክር እያለ እኛንም ያነቃቃናል::

ምድርን ቸል በማለት ሰማይን ለማክበር ይወዳል::

አቤቱ ጌታ ሆይ ይህን ወጣት ሰው ውድ የሆኑትን ቤተሰቦቹንም ሁሉ በፈቃድህ ፍጥነት በምህረትህ ብዛት በፍቅርህም ጉልበት  በሰማይ እና በምድር በረከት በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ባርከው::

ስምህ ለዘለዓለም ብሩክ ይሁን ጌታ አምላክ ሆይ::

You Klick Amen.